የ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብስክሌት ሻምፒዮና ዛሬ ተጀመረ

Published on June 25, 2025
38 views

የ2017ዓም የኢትዮጵያ ብስክሌት ሻምፒዮና ዛሬ ተጀመረ።

Dire TOTO ሰኔ ፣ 18 ቀን ፣ 2017ዓም l መቀሌ

በትግራይ ክልል አስተናጋጅነት በኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን አዘጋጅነት አገር አቀፍ የብስክሌት ሻምፒዮና ውድድር በመቀሌ ከተማ በአዋቂዎች ምድብ የግል ክሮኖ ሜትር ( የሰዓት ጨዋታ ) በወንድና በሴት ውድድር ተጀምሯል። 

በሻምፒዮናው  ከድሬዳዋ ሁለት ክለቦች ድሬ ቶቶ ብስክሌት ክለብ ፤ ድሬዳዋ ከተማ ክለብ ፤ ከትግራይ ክልል 5 ክለቦች  ፤ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ ሸገር ሲቲ ፤ስልጤ ወራቤ ፤ ኢትዮጵያ ወጣቶች አካዳሚ እና 5 ክልሎች በአጠቃላይ 16 ክለቦችና ክልሎች በውድድሩ ተሳትፈዋል ። 

ውድድሩ  እስከ ሰኔ 22/2017 የሚቆይ ሲሆን በነገው ዕለት 2ኛ ቀን ውሎ በወጣቶች ምድብ በወንድና በሴት የግል ክሮኖ ሜትር ጨዋታ ይቀጥላል።

RELATED

EVENTS

የኢትዮጵያ ብስክሌት ሻምፒዮና ውድድር መቀሌ ሰኔ 18/2017 ዓ.ም

መቀሌ ከተማ | | Tigray | Ethiopia

የቶቶ ክለብን ጨምሮ ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች የሚሳተፉበት የ2017 የኢትዮጵያ ብስክሌት ሻምፒዮና ውድድር በመቀሌ ከተማ...

25

Jun

'25

Wednesday

Read More

View All Events