በ6ኛው መላው የድሬዳዋ ጨዋታ የብስክሌት ክለቦች ውድድር  ድሬ-ቶቶ ክለብ የበላይነቱን ይዞ አጠናቀቀ !

Published on May 11, 2025
31 views

TOTO l ግንቦት 3 ፣ 2017 ዓ.ም 

6ኛው መላው የድሬዳዋ ጨዋታዎች ባለፈው ሚያዚያ 26 ቀን 2017 ዓ.ም የተጀመረው የብስክሌት ክለቦች ውድድር  ዛሬ ግንቦት 03 ቀን 2017 ዓ.ም  የ3ኛው ቀን መርሀግብር ቀጥሎ ተካሂዷል፡፡ 

በ35 ዙር 87 ኪ.ሜ በሸፈነው ርቀት በድሬደዋ ከተማ ልዩ ስሙ ከፖሊስ መምሪያ እስከ ማሪያም ሠፈር  የተካሄደ ነበር፡፡ ሦስቱ የድሬዳዋ የብስክሌት ስፖርት  ክለቦች (ድሬ-ቶቶ ፣ ድሬዳዋ ከተማ እና ድሬዳዋ ፖሊስ) ተሳታፊ የሆኑበት  ውድድር የቶቶ ክለብ ብስክሌተኛው ኤፍሬም ወሉ ሰፊ በሆነ ርቀት ተወዳዳሪዎችን በመምራት አሸናፊ መሆን ችሏል፡፡ 

በውድድሩ ላይ ወጣቱ ኤፍሬም ወሉ ከ18 ዙር ጀምሮ ለብቻው ከፊት ሆኖ በረጅምር ርቀት በመምራት ከኋላ  ሲከተሉት የነበሩትን ተወዳዳሪዎችን ፍፁም በሆነ የበላይነት አጠናቋል፡፡ 

6ኛው መላው የድሬዳዋ ጨዋታዎች ብስክሌት ክለቦች ውድድር የፊታችን ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄድው ጨዋታ  ማሳረጊያውን እንደሚያደርግ ከወጣው መርሀግብር  ላይ መረዳት ተችሏል፡፡

RELATED

EVENTS

6ኛው መላው የድሬዳዋ ጨዋታዎች

ፓሊስ መምሪያና ማሪያም ሰፈር | | Dire Dawa | ETHIOPIA

እሁድ ሚያዚያ 26/2017 6ኛው መላው የድሬዳዋ ጨዋታዎች የብስክሌት ውድድር በመጪው ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ይጠናቀቃል...

04

May

'25

Sunday

Read More

View All Events