6ኛው መላው ድሬዳዋ ጨዋታዎች የብስክሌት ውድድር ሁለተኛ ቀን

Published on May 8, 2025
25 views

በ6ኛው መላው ድሬዳዋ ጨዋታዎች የብስክሌት ውድድር የሁለተኛ ቀን መርሀግብር የድሬዳዋ ፖሊስ ብስክሌተኛው ናትናኤል ጥላሁን 1ኛ በመውጣት ውድድሩን አጠናቀቀ፡: ዛሬ ሚያዚያ 30 ቀን 2017 ዓ.ም የተካሄደው ውድድር የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ነው፡፡
ውድድሩ ከድሬዳዋ እስከ  ኦሮሚያ ክልል ጨለንቆ ከተማ እና ቀርሳ ከተማ ላይ የተጠናቀቀ ሲሆን በአጠቃላይ 120 ኪ.ሜ የሸፈነ ነበር፡፡ 

በውድድሩ የድሬዳዋ ፖሊስ ብስክሌተኛው ናትናኤል ጥላሁን 1ኛ በመሆን አጠናቋል፡፡ የክለብ አጋሩ ብሩክ ፍርድአወቅ  2ኛ እንዲሁም የድሬ ቶቶ ብስክሌተኛው ካሌብ በላይ  3ኛ በመውጣት ውድድሩን ማጠናቀቅ ችለዋል፡፡ 

ባለፈው እሁድ ሚያዚያ 26 ቀን 2017 ዓ.ም የተጀመረው 6ኛው መላው የድሬዳዋ ጨዋታዎች የብስክሌት ውድድር  እስከ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም የሚቀጥል ሲሆን የፊታችን እሁድ ግንቦት 03ቀን 2017 ዓ.ም በድሬደዋ ከተማ ልዩ ስሙ መምሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የጎዳና ላይ የዙር ውድድር የሚካሄድ መሆኑን ከወጣው መርሀግብር ለማወቅ ችለናል፡፡ 

RELATED

EVENTS

6ኛው መላው የድሬዳዋ ጨዋታዎች

ፓሊስ መምሪያና ማሪያም ሰፈር | | Dire Dawa | ETHIOPIA

እሁድ ሚያዚያ 26/2017 6ኛው መላው የድሬዳዋ ጨዋታዎች የብስክሌት ውድድር በመጪው ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ይጠናቀቃል...

04

May

'25

Sunday

Read More

View All Events